Registration Announcement

 ቀን ፡ መጋቢት 17 ፤ 2015 ዓ/ም

ማ ስ ታ ወ ቂ ያ

ለትምህርት ፈላጊዎች

በሰዎች ለሰዎች ድርጅት የአግሮ ቴክኒክና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ለ 2015 የትምህርት ዘመን የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተቀብሎ በቴክኖሎጂ እና በእርሻው መስክ በዲግሪ መርሀ ግብር ማስተማር ይፈልጋል ፡፡

በዚህ በሙያው ከፍተኛ ልምድ ባላቸው መምህራኖች እና የመማር ማስተማሩ ሂደት 70% ተግባር ተኮር በሆነው ተመራጭ ኮሌጅ ውስጥ ለመማር የምትፈልጉ፤ የ2014 ዓ/ም የትምህርት ሚኒስቴር የሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት 50% እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ይጋብዛል ፡፡

በመሆኑም ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟሉ ተማሪዎች፤  

       1ኛ.  ኮሌጁ ቅጥር ግቢ      – Harar

       2ኛ.  ዋናው መ/ቤት        – Addis Ababa PCO Office

ከመጋቢት 18, 2015 ቀን  ጀምሮ እስከ መጋቢት 30, 2015 ድረስ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን ኮፒ ከ1 ጉርድ ፎቶ ግራፍ ጋር በመያዝ ዘወትር በስራ ሰዓት መመዝገብ የምትችሉ ሲሆን ፤  

በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ የማትችሉ በኮሌጁ ድህረ ገጽ http://www.mfmattc.edu.et online መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ያሳውቃል ፡፡ 

ኮሌጁ የተማሪዎችን የኮሌጅ ቆይታ ሙሉ በሙሉ የምግብ የመኝታ አገልግሎት በነጻ የሚሰጥ እና ከወጭ መጋራት ውጭ መሆኑንም ያሳውቃል ፡፡ 

ማሳሰቢያ ፡  በ Online ድህረ ገጻችን ላይ ለሚያመለክቱ ተማሪዎች የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ በሶፍት ኮፒ (በpdf) ፎርማት ለዚሁ በተዘጋጀው ፎርም ላይ መላክ ይኖርባቸዋል ፡፡ 

ኮሌጁ

One thought on “Registration Announcement”

Comments are closed.